top of page

(ኢትዮ 360 - ግንቦት 8/2015) አርበኛ ዘመነ ካሴን በግዴታ ችሎት ለማቅረብ እየተሰራ ነው።


አርበኛ ዘመነ ካሴን በግዴታ ችሎት ለማቅረብ እየተሰራ መሆኑን የኢትዮ 360 ምንጮች ገለጹ።


በተደጋጋሚ አርበኛ ዘመነ ካሴ ፍርድ ቤት ቅረብ ለሚለው ጥያቄ የሰጠው የአልቀርብም ምላሽ የኦህዴዱንም ሆነ የብአዴኑን እቅድ ማክሸፉ ይታወቃል።


ከፌደራል ጀምሮ እስከ ክልል በተደጋጋሚ ሲደረግ የነበረውና አርበኛውን በምን መልኩ ማስወገድ ይችላል በሚለው ስብሰባ ላይ አንዱ መንገድ ዘመነን ፍርድ ቤት ማቅረብ የሚል መሆኑን ኢትዮ 360 በመረጃው ማውጣቱ ይታወሳል።


እናም አሁን ላይ ይሄው አካል በዚህ መልኩ ያስቀመጠውን እቅድ ለማሳካት አርበኛ ዘመነን በግዴታ ፍርድ ቤት ለማቅረብ ተዘጋጅቷል ብለዋል።


በዚህ ሂደት ውስጥ ደግሞ ሁከት በመፍጠርና እሱ የፈጠረው በማስመሰል እርምጃ መውሰድ ነው ይላሉ።


ይህን እቅድ ለማሳካትም በግዴታ ፍርድ ቤት ማቅረብ የሚለው ጉዳይ ከስምምነት ላይ ተደርሶበታል ሲሉ የኢትዮ 360 ምንጮች ገልጸዋል።

Recent Posts

See All

ነሃሴ 18/2015 በሰሜን ሸዋ ሽንፈቱን የተከናነበው የገዳይ ቡድኑ ስብስብ የተረፈውን ሃይሉ ሰብስቦ ወደ አካባቢው መመለሱን የኢትዮ 360 ምንጮች ገለጹ።

በሰሜን ሸዋ አንፆኪያ /መኮይ/ ገና በጠዋቱ ሽንፈቱን የተከናነበው የገዳይ ቡድኑ ስብስብ የተረፈውን ሃይሉ ሰብስቦ ወደ አካባቢው መመለሱን የኢትዮ 360 ምንጮች ገለጹ። ገና ሳይነጋ ንጹሃንን ሊፈጅ ወደ በአንጾኪያ...

ነሐሴ 18/2015 የዶንጋ ማህበረሰብ መብቱን በመጠየቁ ብቻ እየተሳደደና እየታሰረ ነው ሲሉ የማህበረሰቡ አባላት ገለጹ።

በደቡብ ክልል አዲስ ተመሰረተ በተባለው ክልል ውስጥ ያሉው የዶንጋ ማህበረሰብ መብቱን በመጠየቁ ብቻ እየተሳደደና እየታሰረ ነው ሲሉ የማህበረሰቡ አባላት ለኢትዮ 360 ገለጹ። አዲስ ተቋቋመ በተባለውና ከፍተኛ ቁጥር...

Comments


bottom of page