top of page

(ኢትዮ 360-ግንቦት 8/2015) በኮምቦልቻ የኦህዴዱ ጄነራሎች በሚስጥር እየመከሩ ነው።


በኮምቦልቻ የኦህዴዱ ጄነራሎች በሚስጥር እየመከሩ መሆኑን የኢትዮ 360 የአካባቢው ምንጮች ገለጹ።


ይሄ የጄኔራሎቹ ስብሰባ ቀናትን የወሰደ መሆኑን የሚናገሩት ምንጮቹ ሚስጥራዊ ስብሰባው እየተካሄደ ያለው ደግሞ ሰን ሳይድ በሚባለውና የኦህዴዱ ገዳይ ቡድን መሰባሰቢያ ነው በሚባለው ሆቴል መሆኑንም ይናገራሉ።


በሆቴሉ ያሉ ክፍሎችን ሁሉ አዘግቶ በሚስጥር እየመከረ ያለው ይሄው የኦህዴዱ ጄኔራሎች ስብስብ የጀመረውና ወደ አማራ ክልል የላከው ሃይሉ ሽንፈትን መከናነቡን ተከትሎ ነው ይላሉ።


አብይ አህመድ በአማራ ክልል ህዝብ ላይ ሊፈጽም ያለው የዘር ማጥፋት ወንጀል አለመሳካቱን ተከትሎ አዲስ ዘመቻ ለመክፈት ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ኢትዮ 360 በተደጋጋሚ በመረጃው ማውጣቱ ይታወሳል።


ቀናትን የወሰደው የኦህዴዱ ጄኔራሎች የሚስጥር ስብሰባም የዚሁ አንድ አካል መሆኑን ሳይጠቁሙ አላለፉም።


ሚስጥራዊ ስብሰባው መቼ እንደሚጠናቀቅ ባይታወቅም ነገር ግን ከዚህ ስብሰባ መጠናቀቅ በኋላ በሁሉም አቅጣጫ ከበንዋል ብለው በሚያስቡት የአማራ ህዝብ ላይ አዲሱን የማጥቃት ዘመቻ ሊጀምሩ ይችላሉ ሲሉም ግምታቸውን አስቀምጠዋል።


በዚህ ምስጥራዊ ስብሰባ ላይ ደግሞ ተልእኮ የሚሰጣቸው የብአዴን ብልጽግና ካድሬዎች መኖራቸውንም ነው የኢትዮ 360 የአካባቢው ምንጮች የሚናገሩት።

Recent Posts

See All

ነሃሴ 18/2015 በሰሜን ሸዋ ሽንፈቱን የተከናነበው የገዳይ ቡድኑ ስብስብ የተረፈውን ሃይሉ ሰብስቦ ወደ አካባቢው መመለሱን የኢትዮ 360 ምንጮች ገለጹ።

በሰሜን ሸዋ አንፆኪያ /መኮይ/ ገና በጠዋቱ ሽንፈቱን የተከናነበው የገዳይ ቡድኑ ስብስብ የተረፈውን ሃይሉ ሰብስቦ ወደ አካባቢው መመለሱን የኢትዮ 360 ምንጮች ገለጹ። ገና ሳይነጋ ንጹሃንን ሊፈጅ ወደ በአንጾኪያ...

ነሐሴ 18/2015 የዶንጋ ማህበረሰብ መብቱን በመጠየቁ ብቻ እየተሳደደና እየታሰረ ነው ሲሉ የማህበረሰቡ አባላት ገለጹ።

በደቡብ ክልል አዲስ ተመሰረተ በተባለው ክልል ውስጥ ያሉው የዶንጋ ማህበረሰብ መብቱን በመጠየቁ ብቻ እየተሳደደና እየታሰረ ነው ሲሉ የማህበረሰቡ አባላት ለኢትዮ 360 ገለጹ። አዲስ ተቋቋመ በተባለውና ከፍተኛ ቁጥር...

Comments


bottom of page