top of page

(ኢትዮ 360-ግንቦት 24/2015) የኢትዮጵያ እስልምና እምነት ተከታዮች እየተሳደዱና እየታሰሩ ነው።


የኢትዮጵያ ሙስሊም ማህበረሰብ ነገ በድጋሚ ተቃውሞ ሊያስነሳ ይችላል በሚል በርካታ የእምነቱ ተከታዮች እየታሰሩ መሆኑን የኢትዮ 360 ምንጮች አስታወቁ።


ከኦህዴዱ ስርአት ህገወጥ የቤትና መስጂድ ፈረሳ ጋር በተያያዘ ነገ ከጁምአ ስግደት በኋላ ተቃዉሞ ይኖራል በሚል በፍርሃት እየራደ ያለው አካል ምናልባትም ነገ የጁምአ ጸሎት እንዳይኖር ሊከለክል ይችላል ሲሉም ዛሬ ላይ እየታየ ያለውን አዝማሚያ አመልክተዋል።



ሌላዉ ይላሉ ምንጮቹ በነገዉ ዕለት መርካቶ ሙሉ ህንፃዎች ላይ ስራ የለም በሚል መደብራቸውን እንዲዘጉ አስገዳጅ ትዕዛዝ መሰጠቱንም ተናግረዋል፡፡


ከዛም አልፎ ስራ የለም የሚል የማስጠንቀቂያ ወረቀቶች በየህንፃዎቹ እየለጠፈ ያለው አካል በየቦታው ካሜራዎችን ገጥመናል የሚሉ መልዕክቶችን በመለጠፍ ላይ መሆኑንም ሳይጠቁሙ አላለፉም።


ይሄንን ሁሉ ማስፈራሪያ እየሰጠ ያለውና በፍርሃት ሊፈርስ የደረሰው የኦህዴዱ አገዛዝ ያሰማራው ቡድን ቤት ለቤት ሳይቀር ዋና ናቸው የሚባሉ የእምነቱ ተከታዮችን እያሳደደ መሆኑን ነው የኢትዮ 360 ምንጮች የተናገሩት።

Recent Posts

See All

ነሃሴ 18/2015 በሰሜን ሸዋ ሽንፈቱን የተከናነበው የገዳይ ቡድኑ ስብስብ የተረፈውን ሃይሉ ሰብስቦ ወደ አካባቢው መመለሱን የኢትዮ 360 ምንጮች ገለጹ።

በሰሜን ሸዋ አንፆኪያ /መኮይ/ ገና በጠዋቱ ሽንፈቱን የተከናነበው የገዳይ ቡድኑ ስብስብ የተረፈውን ሃይሉ ሰብስቦ ወደ አካባቢው መመለሱን የኢትዮ 360 ምንጮች ገለጹ። ገና ሳይነጋ ንጹሃንን ሊፈጅ ወደ በአንጾኪያ...

ነሐሴ 18/2015 የዶንጋ ማህበረሰብ መብቱን በመጠየቁ ብቻ እየተሳደደና እየታሰረ ነው ሲሉ የማህበረሰቡ አባላት ገለጹ።

በደቡብ ክልል አዲስ ተመሰረተ በተባለው ክልል ውስጥ ያሉው የዶንጋ ማህበረሰብ መብቱን በመጠየቁ ብቻ እየተሳደደና እየታሰረ ነው ሲሉ የማህበረሰቡ አባላት ለኢትዮ 360 ገለጹ። አዲስ ተቋቋመ በተባለውና ከፍተኛ ቁጥር...

Comments


bottom of page