top of page

(ኢትዮ 360- ግንቦት 24/2015) ለኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከህብረተሰቡ የተዋጣው ገንዘብ ለቤተመንግስት ግንባታ ሊወሰድ ነው።



ለኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከህብረተሰቡ የተዋጣውን ገንዘብ ለቤተመንግስት ግንባታ በሚል ሊወሰድ መሆኑን የኢትዮ 360 የውስጥ ምንጮች ገለጹ።



ለ12 አመት ያህል ለህዳሴ ግድብ በሚል ከህብረተሰቡና በውጭ ካለው ኢትዮጵያዊና ትውልደ ኢትዮጵያዊ ከፍተኛ ገንዘብ ሲዋጣ መቆየቱን ያነሳሉ።



አሁን ላይ ታዲያ በዋና ሌብነት ላይ የተሰማራው የብልጽግናው ስርአት ይሄን ገንዘብ ለቤተመንግስት ግንባታ በሚል ለመውሰድ ዝግጅቱን ጨርሷል ባይ ናቸው።



ለዚህ ሌብነት እንዲያግዝ ደግሞ ይሄ የግድብ ግንባታ ከተጀመረ ጀምሮ ያለምንም የደሞዝ ጭማሪ ሲሰሩ የነበሩ ባለሙያዎችና ሰራተኞችን ለማባረርም እቅድ ተያዟል ብለዋል።



ይሄንን እቅዳቸውን ለማሳካትም በተለያየ መንገድ ሰራተኛውን ማማረርና ከዚህም ጋር ተያይዞ ስራውን እንዲለቅ እየተደረገ መሆኑንም ሳይጠቁሙ አላለፉም።



በተደጋጋሚ ኢትዮ 360 በመረጃው ከህዳሴው ግድብ ግንባታና ከሰራተኛው ጋር በተያያዘ የኦህዴዱ ስርአት የሰራቸውንና እየሰራቸው ያሉ ወንጀሎችን ሲያጋልጥ መቆየቱ ይታወሳል።



አሁን የህዳሴው ግድብን ገንዘብ በመመዝበርና ሰራተኛውን ከስራ ገበታ ለማባረር የተያዘው እቅድም የዚሁ ወንጀል አንዱ አካል መሆኑን ምንጮቹ ያስቀምጣሉ።

Recent Posts

See All

ነሃሴ 18/2015 በሰሜን ሸዋ ሽንፈቱን የተከናነበው የገዳይ ቡድኑ ስብስብ የተረፈውን ሃይሉ ሰብስቦ ወደ አካባቢው መመለሱን የኢትዮ 360 ምንጮች ገለጹ።

በሰሜን ሸዋ አንፆኪያ /መኮይ/ ገና በጠዋቱ ሽንፈቱን የተከናነበው የገዳይ ቡድኑ ስብስብ የተረፈውን ሃይሉ ሰብስቦ ወደ አካባቢው መመለሱን የኢትዮ 360 ምንጮች ገለጹ። ገና ሳይነጋ ንጹሃንን ሊፈጅ ወደ በአንጾኪያ...

ነሐሴ 18/2015 የዶንጋ ማህበረሰብ መብቱን በመጠየቁ ብቻ እየተሳደደና እየታሰረ ነው ሲሉ የማህበረሰቡ አባላት ገለጹ።

በደቡብ ክልል አዲስ ተመሰረተ በተባለው ክልል ውስጥ ያሉው የዶንጋ ማህበረሰብ መብቱን በመጠየቁ ብቻ እየተሳደደና እየታሰረ ነው ሲሉ የማህበረሰቡ አባላት ለኢትዮ 360 ገለጹ። አዲስ ተቋቋመ በተባለውና ከፍተኛ ቁጥር...

Comments


bottom of page