top of page

በሃድያ ዞን የመንግስት ሰራተኞች ለተቃውሞ አደባባይ ወጡ። (ኢትዮ 360- ሚያዚያ 11/2015)

በሃድያ ዞን የ3 ወር ደሞዝ ያልተከፈላቸው የመንግስት ሰራተኞች ለተቃውሞ አደባባይ መውጣታቸውን ነዋሪዎቹ ለኢትዮ 360 ገለጹ።


የሶስት ወረዳና የአንድ ከተማ አስተዳደር ሰራተኞች የሶስት ወር ደሞዛቸውን በተደጋጋሚ ቢጠብቁም የሚሰጣቸው ግን ማግኘት እንዳልቻሉ ይናገራሉ። በተለይ ለበአል ገንዘቡ ይገባላችኋል ቢባልም ያም ግን ተግባራዊ መሆን አልቻለም ይላሉ።


በአካባቢው የመልካም አስተዳደር ችግር ቢኖርም በአሁን ሰአት ግን ዋናው ጉዳይ የደሞዝ ጉዳይ ነው ብለዋል ነዋሪዎቹ። በምስራቅ ባደዎች፣በምዕራብ ማዶዎች፣በስራሮ ባደዎችና በሾኔ ከተማ አስተዳደር ላለፉት ሶስት ወራት ደሞዝ ያልተከፈለው ማህብረሰብ አደባባይ ለመውጣት ተገዷል ብለዋል። የመንግስት ሰራተኛው ጥያቄውን ሲያቀርብ ደግሞ ዋና መተላለፊያ የሚባሉ መንገዶችን የሚያገናኘውን ዋና መስመሮችን በመዝጋት ጭምር መሆኑንም ለኢትዮ 360 ገልጸዋል።


ዛሬም ተቃውሞው ሌሎች መንገዶችን በመዝጋት ጭምር ተጠናክሮ መቀጠሉን ነው ነዋሪዎቹ ለኢትዮ 360 የገለጹት። ሾኔ ከምትባለው ከተማ ጀምሮ ዋና የሚባሉ መንገዶችን ሁሉ በማካተት የመንግስት ሰራተኛው ተቃውሞውን ቀጥሏል ብለዋል። የኦህዴዱ መከላከያ ሃይል በሸዋና አካባቢው አዲስ ዘመቻ ለመክፈት ሲዘጋጅ ጎንደርና አካባቢውን ደግሞ በከባድ መሳሪያ አስከብቧል።

Recent Posts

See All

ነሃሴ 18/2015 በሰሜን ሸዋ ሽንፈቱን የተከናነበው የገዳይ ቡድኑ ስብስብ የተረፈውን ሃይሉ ሰብስቦ ወደ አካባቢው መመለሱን የኢትዮ 360 ምንጮች ገለጹ።

በሰሜን ሸዋ አንፆኪያ /መኮይ/ ገና በጠዋቱ ሽንፈቱን የተከናነበው የገዳይ ቡድኑ ስብስብ የተረፈውን ሃይሉ ሰብስቦ ወደ አካባቢው መመለሱን የኢትዮ 360 ምንጮች ገለጹ። ገና ሳይነጋ ንጹሃንን ሊፈጅ ወደ በአንጾኪያ...

ነሐሴ 18/2015 የዶንጋ ማህበረሰብ መብቱን በመጠየቁ ብቻ እየተሳደደና እየታሰረ ነው ሲሉ የማህበረሰቡ አባላት ገለጹ።

በደቡብ ክልል አዲስ ተመሰረተ በተባለው ክልል ውስጥ ያሉው የዶንጋ ማህበረሰብ መብቱን በመጠየቁ ብቻ እየተሳደደና እየታሰረ ነው ሲሉ የማህበረሰቡ አባላት ለኢትዮ 360 ገለጹ። አዲስ ተቋቋመ በተባለውና ከፍተኛ ቁጥር...

Σχόλια


bottom of page