top of page

መስከረም 17/2016 በሰሜን ሸዋ ሚዳ መርሃቤቴ ላይ ገድይ ያደረገ ህዝባዊ ሃይሉ በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎችን ከሰው በላይ ሃይል ነጻማውጣታቸውን ገለጹ


መርጦ ለማርያምን ነጻ ያወጣው ህዝባዊ ሃይል መቅደላ አምባ አምባ ዩኒቨርስቲ ውስጥና በአካባቢው በሚገኝ ካምፕ ውስጥ መሽጎ የነበረውን ይሄንን ሃይል ማጽዳት ተችሏል ብለዋል።


አሁን ላይ ከሁሉም አካባቢ የተባረረው ገዳይ ቡድን አሁን አንድ ቦታ በከተማው ፒያሳ ተብሎ በሚጠራውና ደሴ መውጫ ላይ ብቻ መሆኑን ነው የተናገሩት።


አቃስታ ላይ ወሳኝ የምትባለውን ገነቴን ሙሉ በሙሉ ነጻ ያደረገው ህዝባዊ ሃይሉ ወይና አምባንም ነጻ ማውጣቱን ነው የሚናገሩት።


ሚዳ መርሃቤቴ መራኛ ላይ ህዝባዊ ሃይሉ በወሰደው ርምጃ ሙትና ቁስለኛ የሆነውን ገዳይ ቡድን ጭነው መውሰዳቸውን አስታውቀዋል።


ባለፈው እሁድ መራኛ ላይ ነዋሪውን ስብሰባ ጠርቶ 40 ሰው ብቻ የተገኘለት የገዳዩ ቡድን ስብስብ አስተባባሪ ኮለኔል የማንንም መንደር ወጠጤን በአደባባይ እንሰቅለዋለን በሚል ዛቻ እያሰማ መሆኑንም ተናግረዋል።

ይሄ ዛቻ ዝም ብሎ የሚታይ እንዳልሆነና ይሄንን ተከትሎ ትላንት በንጹሃን መኖሪያ ላይ ሲወስድ የነበረው ርምጃ ማሳያ ነው ብለዋል።

በአካባቢው አሁንም እያስቸገሩ ያሉ ሆድ አደር ስብስቦችን በመረጃና በስም መለየት ተችሏል፣አላርፍ ካሉም ወደ ርምጃ ለመግባት እንደሚገደዱም አስጠንቅቀዋል።


በአካባቢው ያሉና በህበረተሰቡ ተቀባይነት ያላቸው አመራሮችን ወደ መግደልና ህዝባዊ ሃይሉ ገደለ ለማለት የሚሰሩ ስራዎች መኖራቸውንም ሳይጠቁሙ አላለፉም።

Recent Posts

See All

መስከረም 17/2016 በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ።

በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞች እየታደኑና እየታፈኑ መሆኑን ሰራተኞቹ ገለጹ። ሰራተኞቹ እየታፈኑ ያሉት ደግሞ በውስጥ በተሰገሰጉ የሰው በላው ስርአት ሃይሎች ጥቆማ ሰጭነት መሆኑን ለኢትዮ 360...

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ

መስከረም 17/2016 አርሶ አደሮችን በግፍ የረሸነውን ገዳይ ቡድን በአካባቢው ያለው የመብረቅ ብርጌድ ጓሌ ሻለቃ ተከታትሎ በወሰደው ርምጃ ሁሉንም ማጽዳቱን ገለጹ። በጎንደር ዙሪያ ማክሰኝት ወረዳ የጭንጫዬ አርሶ...

መስከረም 17/2016 በቃሊቲ ማረሚያ ቤት እነጎበዜ ሲሳይንና ሌሎቹን የሚሰልል ሰው መመደቡን የኢትዮ 360 ምንጮች ተገለጹ።

በቃሊቲ ማረሚያ ቤት 6ኛ የታሰሩት እነ ጎበዚ ሲሳይ ጋ ወርቁ ደምሴ የሚባል በጣም አደገኛና በማረሚያ ቤቱ የቆየ እስረኛ ወደ እነሱ ክፍል እንዲዛወር መደረጉን አስታውቀዋል። ይሄ ግለሰብ ከዚህ በፊት በርካታ ሰዎችን...

Comments


bottom of page